ግድብ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ግድብ ማለት ከመሬት ስር ያለንም ሆነ ከመሬት ላይ (ሸለቆ ውስጥ) የሚፈስን ውሃ ገድቦ ወይንም አንቆ የሚይዝና ሰው ሰራሽ ሃይቅ ለመፍጠር የሚረዳ እንቅፋት ነው። በጐንና በጐን የሚገኙት ሸለቆዎችም የግድቡ አካል ሲሆኑ የሃይቁን የጎንዮሽ ዳርቻዎችን ይወስናሉ። ግድብ የሚለው ቃል የግድብ አካል የሆኑ የግንባታ ክፍሎችን ማለትም እንቅፋት ፈጣሪውን አካል፣ ውሃ የታቆረበትን አካባቢ፣ ውሃውን ለመጠቀም የሚረዱ ግንባታዎችን እንዲሁም የውሃ መጠንን ለመቆጣጠር የሚረዱ ግንባታዎችን ያጠቃልላል። ግድብን ከውሃ መጠን መቆጣጠሪያ (ዊር) የሚለየው ሙሉ በሙሉ ሸለቆውን እንዲዘጋ ተደርጐ የሚገነባ በመሆኑ ነው።