ትምባሆ
From Wikipedia, the free encyclopedia
ትምባሆ ኢትዮጵያ ውስጥና በአለም የሚገኝ ተክል ነው።
ትምባሆ በአሜሪካዎች ቀይ ሕንድ ባህሎች የተቀደሠ እፅ ነው፤ ያጨሰው ሀሣቦች በጢሱ ወደ ሰማይ ይደርሳሉ በማለት ያምናሉ። በባህላቸውም ውል ወይም ንግድ በማጽደቅ እንደ ፊርማ ይጨስ ነበር። በሥነስርዓታቸው ጢስ ወደየአራቱ አቅጣቾች፦ ስሜን፣ ምሥራቅ፣ ደቡብ፣ ምዕራብ፣ ይነፋ ነበር። ሆኖም የተቀደሠ ሲሆን ያለ ሀሣብ በከንቱ ማጨሱ ህመም እንደሚያምጣ ያምናሉ። እንዲያውም ዘመናዊ ሰዎች ያለ ሀሣብ በብዛት ሲያጭሱት ብዙ ህመም ያገኛሉ።