የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ
From Wikipedia, the free encyclopedia
የአሜሪካ ሕገ መንግሥት 22ኛ ማሻሻያ አንቀጽ (Amendment) ለአሜሪካ ፕሬዚዳንት የሚገዙበት ዘመን ቁጥር ይወስናል። እሱ «ማንም ሰው ለፕሬዚዳንት ማዕረግ ከሁለት ጊዜ በላይ አይመረጥም፤ ከሌላ ፕሬዚዳንት ዘመን ከ2 አመት በላይ የጨረሰ ሰውም ከ1 ጊዜ በላይ አይመረጥም» የሚለው የአሜሪካ ሕገ መንግሥት መለወጫ ነው። ይህ መለወጫ በ1943 ዓ.ም. ሕጋዊ ከመሆኑ በፊት በሕገ መንግሥት ዘንድ አንድ ሰው እንደ ፕሬዚዳንት በሚመረጡባቸው ዘመናት ቁጥር ምንም ወሰን አልነበረም። ከፍራንክሊን ሮዘቨልት አስቀድሞ ማንም ሰው ከ2 ጊዜ በላይ አልተመረጠም ነበር። ፍራንክሊን ሮዘቨልት ግን 4 ጊዜ ተመረጡ። ከሳቸው በኋላ ነው ሕጉ የተለወጠ።
ሕገ መንግሥት ለመለውጥ እንዳለው ሥራት የአሜሪካ ምክር ቤት በመጋቢት 15 ቀን 1939 ዓ.ም. ሃሣቡን አቅርቦ በክፍላገሮች በአስፈላጊው ቁጥር በየካቲት 20 ቀን 1943 አጸደቁትና ወዲያው ሕግ ሆነ።