ታላቁ ሳርጎን
From Wikipedia, the free encyclopedia
ታላቁ ሳርጎን (አካድኛ፦ ሻሩ-ኪን «ዕውነተኛ ንጉሥ») ከ2077 እስከ 2064 ዓክልበ. ግድም ድረስ (ኡልትራ አጭር አቆጣጠር) የአካድ ንጉሥ ነበረ።
የሱመር ነገሥታት ዝርዝር ቅጂዎች ለ56፥ 55 ወይም 54 ዓመታት እንደ ገዛ ቢሉንም፣ በሥነ ቅርስ ከዘመኑ የተገኙት ሰነዶች ለአራት ልዩ ልዩ ዓመቶች ብቻ ተገኝተዋል። ስለዚህ በጣም ረጅም ዘመን እንደ ገዛ አጠራጣሪ ነው።
የታወቁት 4 ዓመት ስሞች እንዲህ ናቸው፦ «ሳርጎን ወደ ሲሙሩም የሄደበት ዓመት»፣ «ሳርጎን ኡሩአን ያጠፋበት ዓመት»፣ «ሳርጎን ኤላምን ያጠፋበት ዓመት»፣ እና «ማሪ የጠፋበት ዓመት» ናቸው።[1] ይህ የዓመት ስሞች አቆጣጠር ዘዴ የሚታወቀው በዋናነት ከሳርጎን ዘመን ጀምሮ ነው።